የጥሪ ማስታወቂያ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የተከበራችሁ በሊባኖስ ቤይሩትና እንዲሁም በመላው ዓለም የምትኖሩ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ
በእግዚአብሔር ፍጹም ሰላምታ ሰላም እላችኋለሁ፤ «ወደ ተራራው ውጡ፤ እንጨትንም አምጡ፤ ቤቱንም ሥሩ፤ እኔም በርሱ ደስ ይለኛል፤ እኔም እመሰገናለሁ፤ ይላል የሠራዊት ጌታ!» ትንቢተ ሐጌ ምዕራፍ 1$8 ከጥቅሱ እንደምንረዳው ለአምልኮት የምንገለገልበትን ቤተ ክርስቲያን እንድንሠራው የተነገረ ኃይለ ቃል ነው፤ በመሆኑም በሊባኖ ቤይሩት የደብረ ሲና ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በ1997 ዓ.ም የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ በ2001 ዓ.ም ተፈጽሞ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሮ እነሆ እስካሁን ድረስ ሰፊ አገልግሎት እየተሰጠበት ይገኛል፤ ቤተ ክርስቲያኗ ከምትሰጣቸው መንፈሳዊ አገልግሎቶች መካከል የክርስትና እምነት ተከታዮችና የሌላ እምነት ተከታዮች ምእመናን በቦታው እየተገኙ ጸበል በመጠመቅ ፈውስ እያገኙ መሆናቸው ይታወቃል፤ ነገር ግን አሁን ባላሰብነው ሰዓትና ጊዜ ከቤተ ክርስቲያኑ በስተምዕራቡ በኩል ያለውን ክፍት ቦታ ግለሰብ ገዝቶ የግንባታ ፈቃድ አውጥቶ እየገነባ ይገኛል፤ ይህ ቦታ በግለሰብ እጅ ከሆነ ቤተ ክርስቲያኗ የምትሰጠውን የኪዳን አገልግሎትና የቅዳሴ አገልግሎት፣ የማኅሌት አገልግሎትና የዝማሬ አገልግሎት እንዲሁም የጸበል ማጥመቅ፣ ክርስትና የማስነሳትና የመሳሰሉትን አጠቃላይ መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ማስኬድ የማይቻልበት ሁኔታ ይፈጠራል፤ በመሆኑም ደረጃውን ጠብቆ የካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ቦታው እንድንገዛው ለብፁዕ አባታችን አቡነ ድሜጥሮስ በማሳሰብ ብፁዕነታቸውም የሰበካ ጉባኤውን ሀሳብ ተቀብለው ቦታው እንዲገዛ መልካም ፈቃዳቸውን ገልጸውልናል፤ በመሆኑም ጉዳዩ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ ኮሚቴ አቋቁሞ ቦታውን ለመግዛት ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ ይገኛል፡፡
ስለዚህ «በውኑ ይህን ቤት ፈርሶ ሳለ እናንተ ራሳችሁ በተሸለሙ ቤቶቻችሁ ለመኖር ጊዜው ነውን» ይላል ትንቢተ ሐጌ ምዕራፍ 1$4 የተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች ልጆቻችን ምእመናን ወምእመናት ይህን ቦታ ለመገዛት የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ እያሳሰብን ሃምሳ ሎሚ ለአንድ ሰው ሸክሙ ነው፤ ለሃምሳ ሰው ጌጥ ነው እንደሚባለው ሁሉ እናንተም ይህን ድምጽ ሰምታችሁ የተለመደ ትብብራችሁን እንድታደርጉልን ስንል በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንጠይቃለን፡፡
እግዚአብሔር ሥራችንን ይባርክልን!